free book gift

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።


Iqra

=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=

ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ


1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።

2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።

3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።

4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
Iqra
Iqra

Homeየወጣቱ ተልዕኮ ምንነትየአቂዳ ትምህርቶችየሶላት መመሪያረመዷንሙስሊም ሴቶችኢስላማዊ ቤተሰብከታሪክ ማህደርሐዲስለወጣቶችትምህርትና መሰረታዊ ክህሎታችጤናችንግጥምጥያቄና መልስኢስላማዊ መዝገበ ቃላት
free book gift

=<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=

ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!

free book gift

በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።

free book gift

☀:."•..♥♥የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ♥♥"•.☀:.


553768 247407885426462 553920069 n

- የቀደምት ሂወታቸው

- የትውልድ ቦታ

- የዘር ግንድ

- የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) እናትና አባት

- የተባረከው ውልደት

- የጠቡባቸው ቀናቶች

- የአያታቸው መሞት

- ሥራ

- ከኸድጃ(ረ.ዐ) ጋር ያደረጉት ጋብቻ

- በሂራ ዋሻ ውስጥ የሚያደርጉት ልዩ የሆነ አምልኮ(ኢባዳ)


Muhammad saw

☀:."•.♥የትውልድ ቦታ♥"•.☀:.


ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱት የመጀመሪያው ሰው አደም(ዐ.ሰ) የመጀመሪያውን የአምልኮት ቤት የቆመባት የጥንት የሰው ልጅ መኖሪያ ከሆነችው መካ ከተማ ነው። ይህ ከተማ አረቢያ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በአንፀባራቂ አሸዋና ገላጣ ኮረብታዎች የተሸፈነና በቀይ ባህርና በሶሪያ መካከል የሚገኝ ትልቅ የበረሃ መሬት ነው። ይሁንእንጂ በሂጃዝ ክልል ውስጥ ትንሽ ለምለም ቦታ ይገኛል።

የሙስሊሞች የስልጣኔ መፍለቂያ ፣ የአለም የከተሞች እናት የሆኑት መካ ፣ መዲና ጅዳ የሚገኙት በዚሁ ክልል ውስጥ ነው።

☀:."•..♥♥የዘር ሐረግ♥♥"•.☀:.


የታላቁ ነብይ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የዘር ሐረግ

ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱት የአብዱል ሙጦሊብ ልጅ ከሆነው አብዱሏህ ነው። አብዱል ሙጦሊብ የሐሽም ልጅ ፣ የአብድ መናፍ ልጅ ፣ የቁሰይ ልጅ ፣ የቂላብ ልጅ ፣ የሙራህ ልጅ ፣ የካእብ ልጅ ፣ የሉዋእ ልጅ ፣ የጋሊብ ልጅ ፣ የፋህር ልጅ ፣ የማሊክ ልጅ እያለ እስከ አድናን ልጅ ድረስ ይደርሳል።

የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የዘር ሐረግ ከነብዩ ኢብራሂም ልጅ(ዐ.ሰ) ታላቅ ልጅ ከሆኑት ከነብዩ ኢስማኢል(ዐ.ሰ) እንደሚጀምር ሁሉም ሙስሊሞች እና ትክክለኛ የታሪክ ፀሃፊያኖች የሚስማሙበት ነው።

☀:."•..♥♥የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) አባት♥♥"•.☀:.


የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የተከበሩት አባታች ስም አብዱላህ ሲሆን ትርጉሙም የአሏህ ባሪያ ማለት ነው። እሳቸውም መልከ መልካም ፣ የትልቅ ስብዕና ባለቤት ግንባራቸው ጥልቅ የሆነ ብርሃን የሚያንፀባርቅ የነበሩ የአብዱል ሙጠሊብ ልጅ ናቸው። የሞቱትም በሃያ አምስት አመታቸው ሲሆን በዚያን ጊዜ ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ከናታቸው ማህፀን ነበሩ።
☀:."•..♥♥የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) እናት♥♥"•.☀:.

የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የእናታቸው ስም አሚና ነው። አሚና የወሐብ ልጅ ሲሆኑ ወሐብ ደግሞ የሐሽም ልጅ ናቸው። እናታቸው በቁንጅናቸው ፣ በደግነታቸው ፣ በትሁትነታቸው ፣ በቅዱስነታቸው ይታወቃሉ። እሳቸውም ሲሞቱ ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የ6 አመት እድሜ ልጅ ነበሩ።
☀:."•..♥♥የረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ውልደት♥♥"•.☀:.

የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ውልደት በድቅድቅ ጨለማ ተውጦ ለነበረው አለም ብርሃን ሆኗል። የአረቢያ ምድር በሃጢያትና በጥንቆላ ፅልመት ተዘፍቆ በነበረው በዚህ በሚያስጠላ ዘመን የረሱል(ሰ.ዐ.ወ) በመካ ከተማ ውስጥ መወለድ ለአለም ብርሃን ሆኗል። ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱት በመጀመሪያው አመል ፊል(የዝሆኖች) ጦርነት አመት በ12ኛው ረቢኡል አወል እንደ አውሮፓ አቆጣጠር 570 በተወለዱ በሰባተኛው ቀን በማለዳ ፀሀይዋ ከመውጣቷ በፊት ለአሏህ ምስጋና ለማድረስ የእርድ ስነ-ስርአት ተካሄደ። ሁሉም የቁረይሽ ማህበረሰብ ወደ ድግሱ ተጠራ ፤ ሰዎቹም የልጁ ስም ማነው? ብለው በጠየቁ ጊዜ አያታቸው አብዱል ሙጠሊብ ሙሐመድ ሲሉ መለሱላቸው። ከተለመደው ስም አፈንግጠው ይህን ቅዱስና ልዩ የሆነ ስም ለዚህ ልጅ ለምን እንደተሰጠው ጠየቇቸው። እሳቸውም የኔ ልጅ የሙሉ አለም ምስጋና አድናቆት ይገባዋል ሲሉ መለሱላቸው። ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ማለት በጣም ምስጉን ማለት ነው። የመካ እምነተ ቢሶች ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ከአንድ ንጉስ መወለድ አለበት ሲሉ ተቃወሙ። የአሏህ ምርጫ ግን ሙሐመድ ቢን አብዱ ሏህ ነበሩ።


☀:."•..♥♥የጠቡባቸው ቀናቶች♥♥"•.☀:.

ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) በጣም ደግ ለሆነችው ሐሊማ እንድታጠባቸው በአደራ መልክ ተሰጠች። ህፃኑንም ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ማጥባት በጀመረች ጊዜ የቻለችውን ያህል በሁለቱም ጡቶቿ ለማጥባት ስትሞክር እሳቸው ግን በግራ ጡቷ በፍፁም ጠብታ ታህል አይጠቡም። ይህ ነው እንግዲህ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) እንዴት የሐሊማን ልጅ መብት ገና በህፃንነት እድሜያቸው የጠበቁት። ሁለት አመት ያህል ካጠባቻቸው ቡሃላ መልሳ ወደ እናታቸው መለሰቻቸው። ነገር ግን እናታቸው መልሰው እንደገና እስከ ስድስት አመታቸው ድረስ በዚያ ንፁህ በሆነው የአረብ ጐሳቸው ማህበራዊ አድርጋ እንድታሳድጋቸው በድጋሚ በአደራ መልክ ተሰጣት።


☀:."•..♥♥የአያታቸው ሞት♥♥"•.☀:.

አያታቸው አብዱል ሙጦሊብ ሲሆኑ የሞቱት ነብዩ መሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የስምንት አመት እድሜ ልጅ እያሉ ነው። አያታቸው በጣም የተከበሩ የመካ መሪ እና የካዕባ ጠንካራ ጠባቂዎች ናቸው። እሳቸውም የሞቱት በ84 አመታቸው ሲሆን አያታቸው ለነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) በጣም ተወዳጅና ብቸኛው የአብዱሏህና የአሚና ልጅ መልከ መልካም የሙትልጅ ስለነበሩ በጣም ጥልቅ ፍቅር ነበራቸው።


☀:."•..♥♥የአቡጧሊብ ደጋፊነት♥♥"•.☀:.


አቡጧሊብ: በጣም ተወዳጅ የሆኑት የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) አጐት ናቸው። የረሱል(ሰ.ዐ.ወ) አያት ከመሞታቸው በፊት ለአቡጧሊብ ተንከባክቦ እንዲያሳድጋቸው በአደራ መልክ ሰጧቸው። አቡጧሊብ አሁን ሃላፊነቱ ተቀብለው ተንከባክበውና ማህበራዊ አድርገው በጥልቅ ፍቅርና ውዴታ አሳደጓቸው። በዚህ ጊዜ ነበር ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) የንግድን ጥበብ የተማሩት።


☀:."•..♥♥ሥራ♥♥"•.☀:


ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ወጣት ሲሆኑ በቤተሰብ ስራ ላይ አዘነበሉ። ነገር ግን ምንም ገንዘብ አልነበራቸውም። ታላቇ ሴት ኸድጃ በጣም ሃብታም ነጋዴ ስትሆን ለተወሰነ ጊዜ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) የንግድ ሸቀጦችን በአደራ መልክና በተቆጣጣሪነት በአጐታቸው በኩል የተሰጡ ሲሆን ኸድጃም በታማኝነታቸው ፣ ባማረ ስብዕናቸው ፣ በኑሮ ዘዴያቸው ፣ በግብይት ስርአታቸውና ከሰው ጋር ባለቸው ቅርርብ ትደመም ነበር። እናም እሷ እራሷ ለንግድ ሸቀጦቿን ይዘውላት እንዲሄዱ ጠየቀቻቸው። አብዛኛውን ስራዎቿን ለሳቸው ሰጠች። ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ከዚህ ብኋላ ታማኝና ታላቅ የንግድ ሰው ሆኑ። በንግዳቸውም ብዙ ማትረፍ ጀመሩ። ኸድጃም በታላቅነታቸው ፣ በታማኝነታቸው ፣ በግብይት ስርአታቸው መደመሟን ቀጥላለች።


☀:."•..♥♥ከኸድጃ ጋር ያደረጉት ጋብቻ♥♥"•.☀:.


የኸድጃ(ረ.ዐ) አገልጋይ የነበረው መይስራህ በግብይት ወቅት ከረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ጋር ይሆን ነበርና ሁልጊዜም ለኸድጃ የረሱልን ታላቅ ባህሪ ፣ ለጋስነትና ጨዋነት ይተርክላት ነበር። ይህን ድንቅ ያማረና ታላቅ ስብዕናና ቅድስና በመስማት ኸድጃ(ረ.ዐ) ረሱልን(ሰ.ዐ.ወ) ለጋብቻ ጠየቀች። በጋብቻው ወቅት ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የ25 አመት መልከመልካም ወጣት የነበሩ ሲሆን ኸድጃ(ረ.ዐ) ደግሞ 40 አመቷ ነበር። ከነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ጋር ከተጋባች ለ25 አመት ያህል ኑራለች። ይህን ተከትሎም ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) የጠቅላላ ስራዎቿ ተቆጣጣሪ ሆኑ። ሁሉንም ጊዜያቸውን ኃያሉ አሏህን በመገዛትም ያሳልፉ ነበር።


☀:."•..♥♥በሂራ ዋሻ ውስጥ የሚያደርጉት አምለኮተ አሏህ♥♥"•.☀:.

የመካ ሙሽሪኮች እምነተ ቢሶች ነብዩ ሙሐመድን(ሰ.ዐ.ወ) ተስፋ ለማስቆረጥ ያልጣሩትና ያላደረጉት ነገር የለም። ይሁን እንጂ በሂራ ዋሻ ጧት ማታ እዛው በመሆንና ምግብና ውሃ ይዘው በመሄድ የአምልኮት ተግባራቸውን ጀመሩ። የሂራ ዋሻ ከመካ በስተቀኝ አቅጣጫ በኩል ከሚገኘው የኑር ተራራ ላይ ያለ ሲሆን እዚህ ዋሻ ውስጥ ነበር ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ያለማቇረጥ አሏህን ይገዙና ይለምኑ የነበረው። ምግብና ውሃቸው ካለላለቀ በቀር ወደ ከተማይቱ አይመለሱም።

ይቀጥላል......


Next
የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ ክፍል 1
የነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ ክፍል 2
21524

የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
free book gift

Download Islamic Books
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ

Important Web Links


free book gift

free book gift

free book gift

ስለወጣቱ ተልዕኮ ምንነት ለማወቅ እዚህ ላይ ክሊክ ያድርጉ

Copyright©Youth-Mission የወጣቱ ተልዕኮ


Pair of Vintage Old School Fru